top of page

ጳጉሜ 3 2017 - ታክሲዎች ምሽት ላይ የሚያደርጉት ህገወጥ የታሪፍ ጭማሪ አላስፈላጊ ወጪ እያስወጣቸው እንደሆነ ተጠቃሚዎች ነግረውናል

  • sheger1021fm
  • Sep 8, 2025
  • 1 min read

የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች ምሽት ላይ የሚያደርጉት ህገወጥ የታሪፍ ጭማሪ አላስፈላጊ ወጪ እያስወጣቸው እንደሆነ ተጠቃሚዎች ነግረውናል፡፡


የስምሪት መስመሩን መደበኛ ታሪፍ በእጥፍ የሚያስከፍሉ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች እንዳሉም ሰምተናል፡፡


ያነጋገርናቸው የታክሲ አገልግሎት ሰጪ አሽከርካሪዎች በበኩላቸው እንዳንድ የስምሪት ተቆጣጣሪዎች ያለፍላጎታችን አምሽተን እድንሰራ ያስገድዱናል፤ ከመሸ ደግሞ ጭነን ስንሄድ እንጂ ስንመለስ ተሳፋሪ ስለማናገኝ የተወሰነ ጭማሪ እናደርጋለን ያም ቢሆን እንደሚባለው የተጋነነ አይደለም ብለውናል፡፡


ስለጉዳዩ የጠይቅናቸው በአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳኛቸው ሽፈራው ምሽት ላይ አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎች ያለ ስምሪት ገደብ ወደየሚገቡበት አካባቢ እየጫኑ እንዲሄዱ ስለፈቀድንላቸው ለታሪፍ ጭማሪው አሽከሪካሪዎቹ የሚያነሱት ምክንያት አሳማኝ አይደለም ይላሉ፡፡


ከተቀመጠለት የታሪፍ ክፍያ በተጨማሪ የጠየቃችሁ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ታርጋ በመያዝ 9417 ላይ በመደወል ጥቆማ መስጠት ትችላላችሁም ተብሏል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..


ንጋት መኮንን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page