top of page

ጥቅምት 9፣2017 - ባንኮች ተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈላቸው ትክክል ነው ወይ?

የተጨማሪ እሴት ታክስ ተሻሽሎ ከወራት በፊት ስራ ላይ መዋሉን ተከትሎ፤ ተጨማሪ እሴት ታክስ የማይከፈልበት የመንግስት አገልግሎት ማግኘት ከባድ ሆኗል፡፡


ለውሃ ፣ ለመብራት፣ ለቴሌኮም አገልግሎትና ለሌላውም ተጠቃሚው 15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲከፍል ይገደዳል፡፡


አሁን የፋይናንስ ተቋማትም ወደዚሁ ሥርዓት እየገቡ ነው፡፡


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈል ከጀመረ ሳምንታት የተቆጠረ ሲሆን ሌሎች ባንኮችም ይቀጥላሉ ተብሏል፡፡


ለመሆኑ ከቆጣቢዎቻቸው 6 በመቶዎቹን ብቻ የብድር ተጠቃሚ የሚያደርጉት በሚጥሉት ከፍተኛ ወለድም በቢሊየን ትርፍ የሚያጋብሱ የሚባልላቸው ባንኮች በዚሁ ጊዜ ቫት ማስከፈላቸው ትክክል ነው ወይ?


የሚያስከትለውስ ስጋት ምንድነው? የፋይናንስ ባለሞያን ጠይቀናል፡፡



ትዕግስት ዘሪሁን


Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page