top of page

ጥቅምት 8 2018 "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ

  • sheger1021fm
  • Oct 18
  • 1 min read

Updated: Oct 22

አዲስ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ እና እንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ በጋራ "ልዩ ባስ" የሚል መጠርያ ያለው ለሀገር አቋራጭ መንገደኞች ዲጂታል የክፍያ ቴክኖሎጂ ዛሬ ማስጀመራቸውን ተናገሩ።


ይህ ቴክኖሎጂ ደንበኞች ወይም ተጓዦች ባሉበት ቦታ ሆነው ወደየሚፈልጉበት አካባቢ ለመጓዝ "የልዩ ባስ" የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም ቲኬታቸውን በኦንላይን መቁረጥ ይችላሉ ተብሏል።

ree

የእንግዳ ትራቭል ቴክኖሎጂ መስራች እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ባንተአብ አብይ እንደተናገሩት ቴክኖሎጂውን ስራ ላይ ለማዋል አራት ዓመት እንደፈጀ እና አገልግሎቱን ከደንበኞች በተጨማሪ የግል ባስ ባለንብረቶች ስራቸውን ለማቀላጣፍ መጠቀም የሚችሉበት ነው ብለዋል።


ይህንን አገልግሎት ደንበኞች ቅንጡ ስልካቸውን በመጠቀም ወደቲኬት መቁረጫ ቦታ ሳይሄዱ ባሉበት ሆነው መቁረጥ እንደሚችሉም ሰምተናል።


የአዲስ ፔይ ፋይናንሻል ቴክኖሎጂ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሻኦል በበኩላቸው ይህ የክፍያ ስረዓት በትራንስፖርቱ ዘርፍ ያለውን ችግር ይቀርፋል ተብሎ እንደታመነበት አስረድተዋል።

ree

እንግዳ ቴክኖሎጂ በ13 የኢትዮጵያ ከተማዎች ቢሮ መክፈቱን እና በ38 ቦታዎች ደንበኞች ቲኬቱን በኦንላይን ቆርጠው መንቀሳቀስ እንደሚችሉ ተነግሯል።


ከ19 በላይ ከሚሆኑ የግል ባሶች ወይም "ልዩ ባሶች" ጋር በጋራ እንደሚሰሩ በማስጀመሪያው መረሃግብር ላይ ሰምተናል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page