top of page

ጥቅምት 6፣2017 - የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET248 አውሮፕላን ድሬዳዋ አየር ማረፍያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ሳለ በአውሮፕላኑ ውስጥ ጢስ መታየቱን አየር መንገዱ ተናግሯል

  • sheger1021fm
  • Oct 16, 2024
  • 1 min read

በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET248 አውሮፕላን ድሬዳዋ አየር ማረፍያ ለማረፍ በዝግጅት ላይ ሳለ በአውሮፕላኑ ውስጥ ጢስ መታየቱን አየር መንገዱ ተናግሯል።


አውሮፕላኑ በድሬዳዋ አየር ማረፍያ በሰላም በማረፍ መንገደኞችን በተለመደው መልኩ ከአውሮፕላኑ ማውረድ መቻሉንም ተጠቅሷል፡፡


አየር መንገዱ ጢሱ የተነሳበትን ምክንያት በማጣራት ላይ መሆኑን አስረድቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተፈጠረው ክስተት መንገደኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።

تعليقات


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page