top of page

ጥቅምት 29፣ 2017 - የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በሰራተኞቼ ላይ የስም ማጥፈት ዘመቻ በከፈቱ አካላት ላይ ክስ መስርቻለሁ አለ

  • sheger1021fm
  • Nov 8, 2024
  • 1 min read

የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በእሳት አደጋ ሰራተኞቼ ላይ የስም ማጥፈት ዘመቻ በከፈቱ አካላት ላይ ክስ መስርቻለሁ አለ፡፡


በመርካቶ #ሸማ_ተራ ተከስቶ በነበረው የእሳት አደጋ፣ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እሳቱን ከመጥፋት ይልቅ በገንዘብ ሲደራደሩ፣ ሲቀበሉ ነበር እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር እንደነበር ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከተማ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ በወቅቱ የተከሰተውን እሳት ለማጥፋት ሲረባረቡ በነበሩ ሰራተኞቻችን ላይ ያለምንም ማስረጃ ስማቸውን ባጠፉትና ተቋሙንም የማጠልሸት ዘመቻ ባካሄዱ የማህበራዊ ሚዲያ ባለቤቶችና ግለሰቦች ላይ #ክስ መስርተናል ሲሉ ለሸገር 102.1 ሬዲዮ ተናግረዋል።


አቶ ንጋቱ #የእሳት_አደጋ ሰራተኞች ሙያቸውን የሚከውኑት እስከ ህይወት መስዋእትነት ድረስ ነው ብለዋል።


ኮሚሽኑ ለፖሊስ ክስ ያቀረበበት የስም ማጥፋት ወንጀል ውጤት ከፖሊስ ምርመራ በኋላ ይፋ እንደሚደረግም አቶ ንጋቱ ማሞ ነግረውናል፡፡


ፍቅሩ አምባቸው


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page