top of page
  • sheger1021fm

ጥቅምት 28፣ 20153 ግዙፍ የሲሚንቶ አምራች ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ለመስራት ፍላጎት አላቸው ተባለ


ጥቅምት 28፣ 2015


3 ግዙፍ የሲሚንቶ አምራች ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ለመስራት ፍላጎት አላቸው ተባለ፡፡


ኢትዮጵያ የማዕድን ሐብቶቿን አውቃ ያወቀችውንም እንድትጠቀመው ያግዛሉ፣ ይረዳሉ የተባሉ ከ90 በላይ የውጪ ኩባንያዎች በማዕድን ኤክስፖ ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሏል፡


ወሬው የተሰማው የማዕድን ሚኒስትር ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ ዛሬ መስሪያ ቤታቸው ያዘጋጀውን የማዕድን ኤክስፖ በተመለከተ ለጋዜጠኞች መግለጫ በሰጡበት ጊዜ ነው፡፡


ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ያላትን ሀብት አውቃ ወደ ምርት ለመቀየር ኤክስፖ አስፈላጊ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡


የውጪ ኩባንያዎች አገር ቤት ያለውን ማዕድን አውቀው ወደ ስራ እንዲገቡና ለሚያነሱትም የፖሊሲና ሌሎች ጉዳዮች ምላሽ ይብራራላችዋል ተብሏል፡፡


ወርቅ፣ ብረት፣ ከሰል እና ሌሎችም የተፈጥሮ ሀብቶች አምርቶ በአገር ቤት ለመጠቀም የተረፈውንም ወደ ውጪ ለመላክ በብርቱ እየተሰራ እንደሆነ ሰምተናል፡፡


ኢትዮጵያ በዓመት በቢሊየን ዶላር ብረት ለማስገባት ታወጣለች ያሉት የማዕድን ሚኒስትሩ ይህንን ለማስቀረት እና ብረትን አገር ቤት ለማምረት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ስራ ላይ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡


ተህቦ ንጉሴ


Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page