top of page

ጥቅምት 27፣ 2017 - ዶናልድ ትራምፕ ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዘዳንት መሆን የሚያስችላቸው ውጤት አግኝተዋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Nov 6, 2024
  • 1 min read

ሪፖብሊካዊው የአሜሪካ ፕሬዘዳንት እጩ ዶናልድ ትራምፕ ቀጣዩ የአሜሪካ ፕሬዘዳንት መሆን የሚያስችላቸው ውጤት አግኝተዋል ተባለ፡፡


ትራምፕ 279 ኢሌክቶራል ኮሌጅ ማግኘታቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡


በምርጫው ለማሸነፍ የሚያስችል 270 ኢሌክቶራል ኮሌጅ ብቻ ነበር፡፡

ይሁንና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸውን የቅድሚያ ውጤቱ አሳይቷል፡፡


የዴሞክራቶቹ ፕሬዘዳንታዊ እጩ ካምላ ሐሪስ ያገኙ ደግሞ 223 ኢሌክቶራል ኮሌጅ መሆኑ ታውቋል፡፡


ሪፖብሊካውያኑ የአሜሪካን የህግ መወሰኛ ምክር ቤት (ሴኔት) አብላጫነት መያዛቸው እንደማይቀር ተገምቷል፡፡



Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page