ሪፖብሊካዊው የአሜሪካ ፕሬዘዳንታዊ እጩ ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሀገሮች መሪዎች እንኳን ደስ ያለዎ እየተባሉ ነው፡፡
ትራምፕን እንኳን ደስ ያለዎ ካሉት መካከል የብሪታንያ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ይገኙበታል፡፡
ትራምፕ በፕሬዘዳንታዊ ምርጫው አሸናፊነታቸው ከምናልባትም በላይ እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡
በፍሎሪዳ ፓልም ቢች ለደጋፊዎቻቸው ታላቅ ድል ተቀዳጅተናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አሜሪካውያን ታላቅ ሀላፊነት ሰጥተውኛ ማለታቸውም ተሰምቷል፡፡
ትራምፕ ከ4 ዓመታት በኋላ ወደ ዋይት ሐውስ የመመለሳቸው ነገር እንደተለየ አጋጣሚ ተፈጥሯል፡፡
ሪፖብሊካውያኑ በህግ መወሰኛው ምክር ቤት አብላጫነቱን መቆጣጠራቸው እንደማይቀር መገመቱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ትራምፕን እንኳን ደስ ያለዎ ሲሏቸው፤ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስትር በፊናቸው አብረን ተባብረን እንሰራለን ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
Comments