ጥቅምት 25፣2017 - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ግብይት ገደብ አነሳ
- sheger1021fm
- Nov 4, 2024
- 1 min read
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሞባይል ገንዘብ ግብይት ገደብ አነሳ።
ገደቡ የተነሳው ለጊዜው እንደሆነና ይህም ከባንክ ወደ #ቴሌ_ብር ለሚደርግ የገንዘብ ዝውውር ብቻ አንደሆነ ሸገር 102.1 ራዲዮ ከምንጮቹ ሰምቷል።
የግል ባንኮችም ይህን እንዲያስፈፅሙ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ አዟል፡፡
መንግስት ወይም #የኢትዮዽያ_ኢንቨስትመንት_ሆልዲንግ ግዙፋን ኩባንያ ኢትዮ ቴሌኮምን 10 በመቶ ድርሻ ወደ ገበያ ማውጣቱ ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ ባንኮች ከአክስዮን ግዢ ጋር በተገናኘ በቀላሉ ገንዘብ እየለቀቁ እንዳልሆነ ተሰምቷል።
የሞባይል ገንዘብ ግብይት ገደብ የተነሳውም ኢትዮ ቴሌኮም ለገበያ ያቀረበውን የአክሲዮን ሽያጭ ሂደቱን እስኪያጠናቅቅ ድረስ ነው ተብሏል።
በተጨማሪም የግል ባንኮች ህዝብ የሚጠይቀው እንዲፈፀምለትና ለኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ግዥ ግብይቶች ከባንክ ወደ ቴሌብር ዝውውሮች ሲጠየቁ እንዲፈፅሙ ተጠይቀዋል።
የኢትዮ ቴሌኮም 10% አክሲዮን ሽያጭ ተከትሎ 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች እየተሸጠ ነው።
ተህቦ ንጉሴ
Comments