top of page

ጥቅምት 23፣2017 - የአንዳንድ የትራንስፖርት መጫኛ እና ማውረጃ ቦታዎች መቀየሩን፤ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ተናግሯል

የአንዳንድ የትራንስፖርት መጫኛ እና ማውረጃ ቦታዎች መቀየሩን፤ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ተናግሯል፡፡


ቢሮው የመጫኛ እና የማውረጃ ቦታዎችን ቀይሬአለው ያለው በመገናኛ አገልግሎት ሲሰጥባቸው የነበሩት ላይ ሲሆን በዚህም:-


በቦሌ ክፍለ ከተማ ፊት ለፊት ሲሰጥ የነበረው፤ ከመገናኛ - ቱሉ ዲምቱ እና ኮዬ ፈቼ አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው መስመሮች አምቼ አጠገብ (ቀደም ሲል ከነበረበት ቦታ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ዝቅ ብሎ) ተቀይሯል፡፡


መገናኛ ውስጥ ተርሚናል ሲሰጡ የነበሩ፤ ከመገናኛ - ቃሊቲ፣ ከመገናኛ - ሳሪስ፣ ከመገናኛ - ጋርመንት መስመሮች በጊዜያዊነት መገናኛ ሙሉጌታ ህንጻ ዝቅ ብሎ አምቼ ፊት ለፊት መንገድ ተዛውሯል፡፡


ከዚህ በፊት ሙሉጌታ ህንፃ አካባቢ ይሰጡ የነበሩ መስመሮች (ከመገናኛ - ገርጂ፣ ከመገናኛ - ጎሮ፣ ከመገናኛ - አያት እና ከመገናኛ - ሰሚት የመጫኛና መውረጃ መስመሮች ወደ ዘርፈሽዋል አካባቢ በተዘጋጀው ጊዜያዊ ተርሚናል ውስጥ በመዛወር በሁሉም ሞዳሊቲ አገልግሎት መስጠት ጀምሬአለሁ ብሏል የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ።

留言


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page