top of page

ጥቅምት 22፣2017 - ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ ደረጃ ትምህርት ጀምሮ፤ የግብረገብ ትምህርት ማስተማር እንደሚኖርባቸው የሚደነግግ ህግ ተረቀቀ

  • sheger1021fm
  • Nov 1, 2024
  • 1 min read

ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ ደረጃ ትምህርት ጀምሮ፤ የግብረገብ ትምህርት ማስተማር እንደሚኖርባቸው የሚደነግግ ህግ ተረቀቀ፡፡


እንደ አንድ መሰረታዊ የትምህርት አይነት ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 6ኛ ክፍል ሁሉም ትምህርት ቤቶች የግብረገብ ትምህርትን እንዲያስተምሩ የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡


በተጨማሪወም ረቂቅ አዋጁ ተማሪዎች ቢያንስ 3 ቋንቋን እንዲማሩ ይደነግጋል፡፡


የአፍ መፍቻ ቋንቋን ከቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ጀምሮ እንደሚሰጥ ረቂቁ ያስረዳል፡፡


የአፍ መፍቻ ቋንቋ ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ ደግሞ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሁም እንደ ማስተማሪያ ቋንቋ ሊያገለግል እንደሚችል ተጠቅሷል፡፡

ትዕግስት ዘሪሁን

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page