top of page

ጥቅምት 22፣2017 - በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም ስርቆትና በግንባታ ወቅት የሚደርስ ጉዳት ለስራዬ በብርቱ እንቅፋት ሆኖብኛል'' የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት

  • sheger1021fm
  • Nov 1, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት፤ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም ስርቆትና በግንባታ ወቅት የሚደርስ ጉዳት ለስራዬ በብርቱ እንቅፋት ሆኖብኛል አለ፡፡


ስርቆት የሚፈፀመው በብዛት በአዲስ አበባ ከተማ መሆኑንም ለሸገር ተናግሯል፡፡


በበጀት ዓመቱ 3 ወራት ብቻ ከ2.7 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ባላቸው መሰረተ ልማቶች ላይ #ስርቆት ተፈፅሞብኛል ብሏል፡፡


ባለፈው ዓመትም የአሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ በተፈፀመ 155 የስርቆት ወንጀል ከ52.6 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ደርሶብኛል ብሏል ተቋሙ፡፡

በወንጀሎቹ ተሳትፈዋል ተብለው ጥፋተኝነታቸው የተረጋገጠባቸው 57 ሰዎች ከአምስት ወር እስከ 18 ዓመት #እስራት ተፈርዶቸዋል ተብሏል፡፡


በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በተገዙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀም ስርቆት ከ5 ዓመት እስከ 20 አመት በደረሰ ፅኑ እስራት የሚያስቀጣ መሆኑም አገልግሎት ሰጭ መ/ቤቱ አስታውሷል፡፡


የብዙሃኑን ጥቅም በሚጎዳ መሰል ስርቆት ላይ የተሰማሩትን ህብረተሰቡ ሃይ በማለት እና እንዲያጋልጥ እንዲሁም ለ #ፀጥታ አካላት ጥቆማ እንዲሰጥ ጠይቋል፡፡


በሌላ በኩል የተለያዩ ተቋማት ግንባታ ሲፈፀሙ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው ብሏል፡፡


ባለፉት 3 ወራትም ከ97,000 ብር በላይ ግምት ባለው ንብረቴ ላይ ጉዳት ደርሷል ብሏል፡፡


በዚህም ምክንያት አገልግሎት የሚቋረጥበትና የሚንገላታ የህብረተሰብ ክፍል ብዙ በመሆኑ ገንቢዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page