ጥቅምት 21 2018 - የሴቶችን ሰላም እና ደህንነት ያስጠብቃል የተባለ ድንጋጌ ኢትዮጵያ ከተቀበለች 25 ዓመት ቢሆንም እስካሁን ተግባራዊ ለማድረግ ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር አዘጋጅታ አላጠናቀቀችም ተባለ
- sheger1021fm
- Oct 31, 2025
- 1 min read
Updated: Nov 3, 2025
የሴቶችን ሰላም እና ደህንነት ያስጠብቃል የተባለ ድንጋጌ ኢትዮጵያ ከተቀበለች 25 ዓመት ቢሆንም እስካሁን ተግባራዊ ለማድረግ ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር አዘጋጅታ አላጠናቀቀችም ተባለ፡፡
ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ድንጋጌዎች መካከል አንዱ እንደሆነም ተነግሯል፡፡
ይህንን ድንጋጌ ኢትዮጵያ ብሄራዊ የድርጊት መርሃ ግብር አጠናቅቃ ተግባራዊ ብታደርግ ሴቶች በተፈጥሮም ይሁን በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚገጥማቸውን ችግር አስቀድሞም ይሁን አደጋው ከደረሰ በኋላ ለመከላከል ይረዳል ተብሏል፡፡
ውሳኔው ወይም አለም አቀፍ ድንጋጌው 13 25 እንደሚባልና ከወጣም 25 ዓመት እንደሆነ ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ለማድማጥ…
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments