top of page

ጥቅምት 21፣2017 - ''ከኢንዱስትሪ መስክ በዚህ ዓመት 12.8 በመቶ እድገት ይጠበቃል'' ጠ/ ሚ ዐቢይ አህመድ ተናገሩ

ከኢንዱስትሪ መስክ በዚህ ዓመት 12.8 በመቶ እድገት ይጠበቃል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡


‘’አሁን ላይ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም 67 በመቶ ማድረስ ተችሏል’’ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘’የኢንዱስትሪ ዘርፉም በተያዘው በጀት ዓመት 12.8 በመቶ እንደሚያድግ ይጠበቃል’’ ብለዋል፡፡


በዚህም ከአምራች ዘርፍ 12 በመቶ እድገት፣ እንዲሁም ከኮንስትራክሽን መስክም 12.3 በመቶ እድገት ይጠበቃል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡


‘’ኢንዱስትሪ በዚህ ዓመት ይህን ያህል እድገት የሚመጣው የተጀመረው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ውጤት እያመጣ ስለሆነ ነው’’ ተብሏል፡፡


ከፋበሪካዎች ጋር የሚያያዝ መብራት፣ ቴሌኮም፣ የመሬት አቅርቦት እና ከባንክ ጋር የሚያያዙ ችግሮች ከሞላ ጎደል ተቀርፈዋል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፡፡


አሁን ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉት ከጉሙሩክ ጋር የሚያያዝ ስራ እንደሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመው ለዚህም ስራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡


በዚህም ዓመት ከፋብሪካ በላይ የሆኑ 72 ፕሮጀክቶች ወደ ገበያ እንደሚገቡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page