top of page

ጥቅምት 20 2018"ሰላም በሌለበት ኢንስትመንትም ሆነ የስራ እድል መፍጠር አይቻልም" ሲሉ የአዲስ አበባ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ ተናገሩ።

  • Oct 30, 2025
  • 1 min read

ፕሬዝዳንቷ ይህ የተናገሩት ዛሬ ጥቅምት 20 ቀን 2018 ዓ.ም "የንግድ ሚና ለሰላም ግንባታ'' በሚል ሃሳብ አዲስ አበባ የንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባሰናዳው የፓናል ወይይት ላይ ነው።


ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንት ሆነ ለሌላ ስራ ሰላም መሰረት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ ያለ ሰላም ንግድን ማሰብ ከባድ እንደሆነ ጠቁመዋል።


የሰላም መስፍን ለሀገር ችግር መፍትሔ ነውም ብለዋል።


የሰላም እጦት ንግድ እንቅስቃሴ  እንዳይኖር፣ ምርት ከቦታ መንቀሳቀስ እንዳይችል ማድረጉን ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ ተናግረዋል።


ሰላም እንዲኖር ደግሞ የመግስት እና የግሉ ዘርፍ ምክክር አስፈላጊ ሲሉ ጠቁመዋል።


የስራ እድል ኢንዲፈጠር፣ ኢንቨስትመንትም ኢንዲበረታታ ደግሞ ሰላም መሰረት መሆኑን የአዲስ አበባ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ዘሃራ ሞሃመድ አስረድተዋል።


የሰላም እጦት የሰው ልጅን፣ ንግድ እና ለኢንቨስትመንት ብቻ ሳይሆን እንስሳት እና እጽዋትም ጭምር የሚጎዳ መሆኑን በአግባቡ መረዳት አስፈላጊ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ጉባዔ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ ናቸው።


ንግድ የሰው ልጆች የሚያግባባበት እና የሚረዳዳበት እንደሆነ ጠቅሰው ምክንያቱ ደግሞ ንግድ አገናኝ ስለሆነ ነው ብለዋል።


ሰው ሲገዛም ሆነ ሲሸጥ ተነጋግሮ፣ ተወያይቶ ነው ያሉት ቀሲስ ታጋይ ሰላም ከሌለ ግን እነዚህ ግንኙነቶች ይቀራሉ መነጋገርም ይቀራል ሲሉ አስረድተዋል።


በኢትዮጵያ ያለው የሰላም እጦት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩን ያስረዱት ፀሃፊው በዚህም ምክንያት ኢንዱስትሪዎች ሲወድሙ ንግድ ሲቋረጥ እያያን ነው ይህን ማስተካካል ያስፈልጋል ይህ ካልሆነ ግን በሌሎች ሰፈር ያየነውን እኛ ጋርም መምጣቱ አይቀሬ ነው ብለዋል።


በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ሃይማኖት ጉባዔ ፀሐፊ ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ የኢትዮጵያ ሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ ( ፕ/ር ) ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች እና የንግዱ ማህበረሰብ ተሳትፈዋል።


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Recent Posts

See All
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም  ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ሃዲዶች ላይ ለአካል ጉዳተኞች የተሰራው መወጣጫ(ራምፕ) ለዓመታት በመዘጋቱ አካል ጉዳተኞች ባቡር መጠቀም ለማቆም ተገደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሃዲዱ ጠባቂ የፀጥታ አካላት የተዘጋውን መወጣጫ(ራምፕ) እንዲከፍቱላቸው ቢጠይቁም የተሰጣቸው ምላሽ እስከ ድብደባ የደረሰ

 
 
 
የነሐሴ 7 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ዩጋንዳ ዩጋንዳ ከአውሮፓ የሚባረሩ የ3ኛ አገር ስደተኞችን ልትቀበል ነው ተባለ፡፡ ዩጋንዳ ከአውሮፓ ተባራሪዎቹን ተቀብላ ለማስተናገድ መዘጋጀቷን ካቲሜሪኒ የተሰኘ የግሪክ ጋዜጣ መዘገቡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ጋዜጣው ዘገባውን ያሰራጨው ዲፕሎማሲያዊ ምንጮችን በዋቢነት በመጥቀስ እንደሆነ ታውቋል፡፡ የሐሳቡ ቀዳሚ አፍላቂዎች

 
 
 
በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ።

ነሐሴ 7 2018 በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ሊከሰት የሚችለው ኤልኒኖ በግብርና እንዲሁም አምራች እና የአገልግሎት ዘርፎች ላይም ተፅዕኖ ይኖረዋል ተባለ። ከአስር ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የታየው የኤልኒኖ ተፅዕኖ የእህል ምርት ውጤትን ከ15 እስከ 20 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎ እንደነበር አንድ የዘርፉ ተመራማሪ ነ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page