top of page

ጥቅምት 20፣2017 - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ነገ በፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ነገ በፓርላማ ቀርበው ማብራሪያ ሊሰጡ ነው፡፡


ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀስላሴ በመስከረም ወር መጨረሻ ለህዝብ እንደራሴዎች እና ለፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ባቀረቡት የመንግስትን ዕቅድ ላይ ማብራሪያ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡


ፕሬዚዳንቱ ያቀረቡትን እቅድ አስታከው የ #ፓርላማ አባላትም ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች ጭምር ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ማብራሪያ የሚሰጡት ተብሏል፡፡


ከፓርላማው ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው ነገ ምክር ቤቱ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባው የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና የአለም አቀፉ ተቋማት ተጠሪዎች እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች ይገኛሉ፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page