top of page

ጥቅምት 20፣2017 - በኢትዮጵያ ጀማሪ የስራ ፈጣሪዎች የሚያስፈልጓቸው ድጋፎች እየተደረጉላቸው አይደለም ተባለ

  • sheger1021fm
  • Oct 30, 2024
  • 1 min read

የቴክኒካል እና የገንዘብ ድጋፍ አለማግኘታቸው ስራ ፈጣሪዎች እንዳይበራከቱ እንቅፋት መሆኑም ተነግሯል፡፡


ስራ ፈጣሪዎች በሚፈለገው ልክ ወደ ፊት አለመውጣታቸው የስራ አጥ ቁጥሩን እንዳይቀንስ አድርጎታል ተብሏል፡፡


ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች የሚያስፈልጋቸውን ቴክኒካል እና የገንዘብ ድጋፍ አለማግኘታቸው ዋነኛው ችግር ነው፡፡


በተጨማሪም ለስራቸው ምቹ ቦታ አለማግኘታቸው፣ የታክስ ሥርዓቱ ለጀማሪ የስራ ፈጠሪዎች የተመቸ አለመሆን እና ሌላ ሌላውም ችግር ወደ ፊት እንዳይወጡ እና በሚፈለገው ልክ ስራ ፈጣሪዎች ወደ ገበያው እንዳይገቡ ያደርጋቸዋል ይላሉ በዘርፉ ላይ የሚሰራው ዊቬንቸር የተሰኘ ድርጅት ስራ አስኪያጅ የሆኑት ማክዳ ፀጋዬ፡፡


ጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች በተገቢው መንገድ አለመታገዛቸው እንደ ሀገር ምን አሳጥቶናል ብለን የጠየቅናቸው የዊቬንቸር መስራች ማክዳ ፀጋዬ የስራ አጥ ቁጥሩ እንዲጨምር ምክንያት መሆኑን ይናገራሉ፡፡


በሌሎች የአለም ሀገራት ከ80 በመቶ በላይ የስራ እድል የሚፈጠረው በጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች መሆኑን የሚናገሩት ማክዳ ፀጋዬ ስራ ፈጣሪዎችን አለመደገፋችን የስራ አጥ ቁጥሩ እንዳይቀንስ አድርጎታል ይላሉ፡፡


ዘርፉ አለበት የተባለውን ችግር ለመፍታትም እየሰራሁ ነው ያለው ዊቬንቸር የተሰኘው ድርጅት ስራ ፈጣሪዎችን መደገፍ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ሥነ ምህዳሩ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ሲነገር ሰምተናል፡፡


ስራ ፈጣሪዎችን በተለያየ መንገድ ድጋፍ እያደረገ ያለው ዊቬንቸር የተሰኘው ድርጅት በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ የገባው ከአመት በፊት ነው፡፡


ፋሲካ ሙሉወርቅ


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page