የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከምክክር ሂደቱ ራሳቸውን ያገለሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት ወደ ንግግር እንዲገቡ የድርሻዬን እንድወጣ መንግስት እና የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጠይቀውኛል አለ፡፡
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሁሉም አካላት ወደ ምክክር እንዲገቡ የድርሻውን እንዲወጣ መጠየቁን አረጋግጧል፡፡
የፖለቲካ ፓርዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ ደስታ ዲንቃ ሀሙስ ዕለት ከምክክር ኮሚሽን ጋር በነበረን ወይይት ከተጠቀሱት አካላት ጋር ተያይዞ ወደ ምክክሩ ባለመግባታቸው ችግሮች መኖራቸውን ነግሮናል ብለዋል፡፡
ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እና በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ አካላት ካልተሳተፉ ወጤታማ የሆነ ምክክር ለማድረግ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችል ኮሚሽኑ ነግሮኛል እኛ ሁሉን ያላካተተ ምክክር ውጤት እንደማያመጣ ለኮሚሽነሮቹ አስረድተናል ሲሉ ሰብሳቢ ተናግረዋል፡፡
አቶ ደስታ ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር ከሆኑት አቶ አደም ፋራ ጋርም በዚሁ ጉዳይ ላይ ሰሞኑን ተነጋግረናል ብለዋል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
Comments