top of page

ጥቅምት 2፣2017 - አክሲዮኖችንግዑዝ አልባ የማድረጊያ ረቂቂ መመሪያ ይፋ ማድረጉን የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 12, 2024
  • 1 min read

ሰነደ ሙዓለ ንዋዮችን (አክሲዮኖችን) ግዑዝ አልባ የማድረጊያ ረቂቂ መመሪያ ይፋ ማድረጉን የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ተናገረ፡፡


መመሪያው ከመጽደቁ በፊት ህዝብ ውይይት እንደሚያደርግበት ተነግሯል፡፡


ከማህበረሰቡ በሚቀርቡ ሀሳቦች ረቂቁን ማዳበር እና ስራው ግልፅ የሆነ የአሰራር ሂደት እንደሚከተል ማሳየት የውይይቱ ዋና አለማ ነው ተብሏል፡፡


ሪቂቅ መመሪያው ላይ ግምገማ እና አስተያየት መስጠት ለሚፈልግ አካላት፤ በሩ ክፍት እንደሆነ ባለስልጣኑ ተናግሯል፡፡


ግምገማ እና አስተያየት የመስጫ ጊዜውም ከዛሬ ጥቅምት 2፣2016 ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡


ባለስልጣኑ፤ ህዝባዊ ውይይቱ ላይ መሳተፍም የሚፈልግ በዚህ አድራሻ (ecma.gov.et) ያሳውቀኝ ያለ ሲሆን በረቅቅ መመሪያው ላይ አስተያየት ለመስጠት ደግሞ (communications@ecma.gov.et) ተጠቀሙ ብሏል፡፡


ማንያዘዋል ጌታሁን

تعليقات


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page