ጥቅምት 19፣2017 - ‘’ገሊላ ማንፋክቸሪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር’’ ያስገነባውን የጫማ ማምረቻ ፋብሪካ አስመረቀ
- sheger1021fm
- Oct 29, 2024
- 1 min read
በቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ፤ ‘’ገሊላ ማንፋክቸሪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር’’ ያስገነባውን የጫማ ማምረቻ ፋብሪካ አስመረቀ።
ፋብሪካው ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት የተገነባ ሲሆን በቀን 2,000 የህፃናት እና የአዋቂ ጫማዎችን እንደሚያመርት ተነግሯል።


ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ስራ ሲጀምር በቀን 4,000 ጫማዎችን እንደሚያመርት ሰምተናል።
የገሊላ ማኑፋክቸሪንግ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ እና ባለቤት አቶ በርሄ አሰፋ ኩባንያው የተለያዩ አይነት ጫማዎችን እንደሚያምርት እና ምርቶቹንም ለሀገር ውስጥ ገበያ ከማቅረብ ባሻገር ወደ ተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት እንደሚልኩም ተናግረዋል።
ሙሉ ዘገባውን በድምፅ ለማድመጥ
ፍቅሩ አምባቸው
Comments