top of page

ጥቅምት 19፣2017 - በኢትዮጵያ ከ3.3 በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃየች እንዳሉ ተነግሯል

  • sheger1021fm
  • Oct 29, 2024
  • 1 min read

በየጊዜው በሚከሰቱ ማንነትን መሠረት ያደረጉ የታጠቁ ቡድኖች ጥቃቶች፤ በመንግሥት እና በታጠቁ ቡድኖች መካከል በሚደረጉ ግጭቶች እና ዘላቂ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ መፍትሔ ባልተሰጠባቸው የወሰን ይገባኛል ጥያቄዎች ምክንያት በሚከሰት ግጭት እና ጦርነት ሰዎችን ከመኖሪያ ቀያቸው ማፈናቀላቸውን ቀጠለዋል ሲል ኢሰመኮ ተናገረ፡፡


በአፋር፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሐረሪ፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ሶማሊ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልሎች ተፈናቅለው እርዳታ ጠባቂ የሆኑ በየመጠለያ ጣቢያው እና ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አንዳሉ ኮሚሽወጣው ሪፖርት አስረድቷል።


በኢትዮጵያ ከ3.3 በላይ የሀገር ውስጥ ተፈናቃየች እንዳሉም ተነግሯል፡፡


ከእነዚህ መካከልም 2.2 ሚሊዮን ገደማዎቹ በግጭት እና ጦርነት የተነሳ የተፈናቀሉ ናቸው ተብሏል፡፡


16 ከሞቶ የሚሆኑት በድርቅ፣ የተቀሩት ደግሞ በአየር ንብረት ለውጥ፣ በልማት እንዲሁም በሌሎች ምክንያቶች የተፈናቀሉ እንደሆኑ ተነግሯል፡፡


ከአጠቃላይ ከሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መካከልም 56 ከመቶ የሚሆኑት ከአንድ ዓመት በላይ በተራዘመ መፈናቀል የቆዩ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በሪፖርቱ አስነብቧል፡፡



ማርታ በቀለ



Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page