ጥቅምት 17፣2016 - ብሪቲሽ ካውንስል ለመምህራን ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተሰምቷል
- sheger1021fm
- Oct 28, 2023
- 1 min read
ጥያቄ ውስጥ የገባው የመምህራን ብቃት ከትምህርት ጥራት መውደቅ እና ከተማሪዎችም ውጤት ማነስ ጋር ቀጥተኛ ተያያዥነት አለው፡፡
መምህራን አለባቸው ከተባሉ ክፍተቶች መካከል የሆነውን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ብቃት ለማሻሻል ብሪቲሽ ካውንስል እስከ 8ተኛ ክፍል ለሚያስተምሩ መምህራን ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
የትምህርት ሚኒስቴርም መምህራንን ብቁ ለማድረግ ከመጭው ክረምት ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ማሰልጠን እንደሚጀምር ተናግሯል፡፡
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz
Comentarios