top of page

ጥቅምት 16፣2017 - የአዲስ አበባን የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት መሸኛቸውን ይዘው የሚጠባበቁ ሰዎች ብዛት 39,000 ደርሷል፡፡

  • sheger1021fm
  • Oct 26, 2024
  • 1 min read

በአዲስ አበባ ሁሉንም የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት በቅድሚያ የብሔራዊ ዲጂታል(ፋይዳ) መመዝገብ ግዴታ እንደሆነ ከአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲው ሰምተናል፡፡


ከተለያዩ አካባቢዎች መልቀቂያ ይዘው የአዲስ አበባ የነዋሪነት አገልግሎት ለማግኘት ከዚህ ቀደም 6 ወር የሚጠብቁ የነበረ ሲሆን አሁን 3 ወር እንደሚጠብቁም ተነግሯል፡፡


ተገልጋዮች ወደ ኤጀንሲው ሲመጡ የተቀመጠውን መስፈርት ባለሟሟላታቸው መልቀቅያ ወይንም መሸኛ አምጥተው እንደሚጠብቁ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ነግረውናል፡፡


ከነዚህ ውስጥ የተቀመጠውን የ3 ወር ጊዜ የማይጠብቁ እና አስቸኳይ የሆነ ምላሽ የሚሰጣቸውም እንዳሉ አስረድተዋል፡፡




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page