top of page

ጥቅምት 11፣2017 - በአማራ ክልል በጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን የጤና አገልግሎት እና የሰብዓዊ ድጋፎች ችግር ይፈታል የተባለ ሰነድ መዘጋጀቱ ተሰማ

  • Oct 21, 2024
  • 1 min read

በአማራ ክልል በጦርነት ምክንያት የተፈጠረውን የጤና አገልግሎት እና የሰብዓዊ ድጋፎች ችግር ይፈታል የተባለ ሰነድ መዘጋጀቱ ተሰማ፡፡


በሰነድ ዝግጅቱ ላይ መንግስትን ጨምሮ የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች መሳተፋቸው ተሰምቷል።


አሁን ላይ በአማራ ክልል ያለው ግጭት መሰረታዊ የጤና አገልግሎቱን ለማከናውን ትልቅ ችግር ሆኗል ተብሏል፡፡


የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ምሁራን ባደረጉት ውይይት ግጭቱ የማህበረሰቡን የጤና አገልግሎት ወደ ውስብስብ ችግር እንዲገባ ምክንያት ሆኗል ብለዋል፡፡


ከዚህ በተጨማሪም ድጋፍ በክልሉ የትኛውም አካባቢዎች እንዳይደርስ አድርጎታል ሲሉ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ ነግሯል፡፡


የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ይህንን ችግር ይፈታል የተባለ ጥናታዊ ሰነድ ማዘጋጀቱን ሰምተናል፡፡፡


የአማራ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ በዛብህ ክልሉ በጤናው ዘርፍ ትልቅ ችግር ውስጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡


ይህም አለማቀፍ ድጋፍን የሚፈልግ ነው ሲሉ አክለዋል።


ባለፉት 5 ዓመታት የአማራ ክልል በሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ በሆነ ችግር ውስጥ መሆኑን ሰሞኑን በተካሄደው የአማራ ክልል የዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ላይ ተነስቷል፡፡


በተዘጋጀው ጥናት ላይ የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የሲቪክ ማህበራት እንዲሁም የህብረተሰብ ጤና ኢኒስቲትዩት በጋራ የተሳተፉበት ነው ተብሏል።


ማርታ በቀለ





Recent Posts

See All
የነሐሴ 4 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ሳውዲ_አረቢያ በሳውዲ አረቢያ ጂዛን በሚገኝ የነዳጅ ማጣሪያ ላይ ከባድ ቃጠሎ ተቅስቅሶ ነበር ተባለ፡፡ በጂዛኑ ማጣሪያ ላይ ቃጠሎ ተቅስቅሶ የነበረው ከባድ ፍንዳታ ከተሰማ በኋላ እንደሆነ አናዶሉ ፅፏል፡፡ በጁቢየል የተፈጥሮ ጋዝ ማሰናጃ ከተማም ቃጠሎ ተቀስቅሶ ነበር ተብሏል፡፡ የሳውዲ ምንጮች ቃጠሎዎቹ ተቀስቅሰው እ

 
 
 
በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡

ነሐሴ 4 2018 በሆነውም ባልሆነውም እየተቀጣን ነው ሲሉ አሽከርካሪዎች ያማርራሉ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት በበኩሉ ሳያጠፋ የምንቀጣው አሽከርካሪ የለም እንዲያውም ሁሉንም ህጎች እናስከብር ብንል የማይቀጣ አሽከርካሪ አይኖርም ብሏል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... ምህረት ስዩም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page