top of page

ጥር 9፣2016 - የመልካም አስተዳደር መርህዎችን መሰረት ተደርጎ በተሰራ ልኬት የማዕድን ሚኒስቴር የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ

አምስት ዋና ዋና የመልካም አስተዳደር መርህዎችን መሰረት ተደርጎ በተሰራ ልኬት የማዕድን ሚኒስቴር የመጨረሻውን ደረጃ ያዘ፡፡


ልኬቱን የሰራው የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ነው፡፡


ልኬቱ የተሰራው በኢትዮጵያ ካሉ 22 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ውስጥ በ15ቱ ነው ተብሏል፡፡


የኢትዮጵያ ሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ልኬቱን ለማሰናዳት 10 ወር እንደፈጀበት ሲናገር ሰምተናል፡፡


መለኪያ መስፈርቶቹ 5 ሲሆኑ እነሱም ውጤታማነት፣ ተጠያቂነት፣ ግልፅነት፣ ፍትሃዊነትና የህግ ተገዥነት ናቸው መባሉን ሰምተናል፡፡


በተሻለ የአፈፃፀም ደረጃ በቅደም ተከተል የጤና፣ የገንዘብ፣ የግብርና፣ የትምህርት፣ የኢንዱስትሪ እና የፍትህ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ተቀምጠዋል፡፡


15ቱም መስሪያ ቤቶች የመረጃን ነፃነት ህግን አለመተግበር የታየባቸው ክፍተት ነው ተብሏል፡፡


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page