top of page

ጥር 8፣ 2015- በቡርኪናፋሶ ሰሜናዊ ግዛት 50 ያህል ሴቶች በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተሰማ


በቡርኪናፋሶ ሰሜናዊ ግዛት 50 ያህል ሴቶች በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸው ተሰማ፡፡


እገታውን የፈፀሙት ፅንፈኞች እንደሆኑ በብርቱ መጠርጠሩን RNZ ሬዲዮ በድረ ገፁ ፅፏል፡፡


ታጣቂዎቹ የ50 ያህል ሴቶች እገታ የፈፀሙት በሰሜናዊቱ አርቢዳንዳ ከተማ ነው ተብሏል፡፡


አገሪቱ የፅንፈኞች የጥቃት ዒላማ ከሆነች ቆይታለች፡፡


ለቡርኪናፋሶ የፅንፈኞቹ ጉዳይ የተቸገረ ነገር የጠፋ ለመላ እየሆነባት ነው፡፡


በዚሁ ተፅዕኖ ምክንያት 2 ሚሊዮን ያህል ሰዎች ለመፈናቀል እንደተገደዱ ይነገራል፡፡


አገሪቱ በቅርቡ ተደራራቢ ወታደራዊ የመንግስት ግልበጣዎች እንደተካሄዱባት ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page