top of page

ጥር 6፣ 2015- M-23 የተሰኘው አማጺ ቡድን ከምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣ በወረራ ከያዛቸው የኢቱሪ ግዛት አካባቢዎች ለቅቆ ለመውጣት ቃል ገባ

  • sheger1021fm
  • Jan 14, 2023
  • 1 min read

M-23 የተሰኘው አማጺ ቡድን ከምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣ በወረራ ከያዛቸው የኢቱሪ ግዛት አካባቢዎች ለቅቆ ለመውጣት ቃል ገባ፡፡


አማፂው ቡድን ከኢቱሪ ግዛት ደረጃ በደረጃ ጠቅልሎ እንደሚወጣ ቃል የገባው ለአካባቢው ዋነኛ የሰላም አመቻች ለኬኒያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ እንደሆነ ዘ ኢስት አፍሪካን ፅፏል፡፡


M-23 ከያዛቸው ግዛቶች ለመውጣት ከመስማማቱ በተጨማሪ ተኩስ አቆማለሁ ማለቱም ተሰምቷል፡፡


ይሁንና የአማፂው ቡድን ታጣቂዎች ከያዟቸው ቦታዎች መቼ ለቅቀው እንደሚወጡ እና ከመቼ አንስቶ ተኩስ እንደሚያቆሙ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የለም፡፡


የኮንጎ ኪንሻሣ መንግስት ጎረቤት ሩዋንዳ የ M-23 አማጺ ቡድን አዝማች ነች ስትል ትከሳለች፡፡


በአሁኑ ወቅት የምስራቅ አፍሪካ ማህበረሰብ አረጋጊ ሀይል በምስራቃዊ ኮንጎ ኪንሻሣ እየሰፈረ ነው፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




留言

無法載入留言
似乎有技術問題。請重新連線或重新整理頁面。
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page