top of page
  • sheger1021fm

ጥር 6፣ 2015- የማዕድን ሚኒስትሩን አቶ ታከለ ኡማ እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ 4 ሚኒስትሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ


የማዕድን ሚኒስትሩን አቶ ታከለ ኡማ እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስን ጨምሮ 4 ሚኒስትሮች ከኃላፊነታቸው ተነሱ፡፡


የሚኒስትሮች ምክር ቤት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሯን ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስን፣ የማዕድን ሚኒስትሩን አቶ ታከለ ኡማ፤ የግብርና ሚኒስትሩን አቶ ኡመር ሁሴን እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ተፈሪ ፍቅሬን ዛሬ ሸኝቷቸዋል።


በሽኝት መርሐ-ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አባላት ተገኝተዋል።


የሚኒስትሮች ምክር ቤት አራቱንም የምክር ቤት አባላት ቀጣይ ጉዟቸው ስኬታማ እንዲሆንላቸው ተመኝቷል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ሚኒስትር ጽ/ቤት ተናግሯል።


አቶ ኡመር ሁሴን እና አቶ ተፈሪ ፍቅሬ በቅርቡ በፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአምባሳደርነት መሾማቸው ይታወሳል፡፡


ንጋቱ ሙሉ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page