top of page

ጥር 5፣2017 - የምልክት ቋንቋ በህግ ደረጃ የተደገፈ አንድ ቋንቋ እንደ ሀገር ሊደረግ እንደሚገባ ተነገረ

  • sheger1021fm
  • Jan 13
  • 1 min read

የምልክት ቋንቋ በህግ ደረጃ የተደገፈ አንድ ቋንቋ እንደ ሀገር ሊደረግ እንደሚገባ ተነገረ፡፡


ኢትዮጵያ ውስጥ ከ5 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መስማት የተሳናቸው ናቸው ተብሎ ይታመናል ተብሏል፡፡


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ጋዜጠኝነትና ኮሚዩኒኬሽን ኮሌጅ ሀላፊ አማኑኤል አለማየሁ (ዶ/ር) #የምልክት_ቋንቋ በታሰበው ልክ እያደገ አይደለም ብለዋል፡፡


ዩኒቨርሲቲው ባለፉት 15 ዓመታት ቋንቋውን ለማሳደግ ከመጀመሪያ ዲግሪ ጀምሮ እስከ 2ተኛ ዲግሪ ድረስ ተማሪዎችን እያሰለጠ ይገኛል ተብሏል፡፡


ነገር ግን ኢትዮጵያ ውስጥ መስማት የተሳነው ዜጋ ቁጥር እና የቋንቋው እድገት የሚመጣጠን አይደለም ሲሉ ዶ/ር አማኑኤል ነግረውናል፡፡


ይህን ክፍተት ለመሙላት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አጫጭር ስልጠናዎች እየሰጠ ይገኛል ያሉት ዶ/ር አማኑኤል አለማየሁ ሥልጠናው ማንኛውም ሰው እንዲማር እያደረግን ነው ብለዋል፡፡

አሁንም ቢሆን የምልክት ቋንቋ እንደ አንድ ቋንቋ አድርጎ የመቀበል ነገር ህብረተሰቡ ውስጥ እንደ ክፍተት እየታየ ነው ብለዋል፡፡


ከነገ ጀምሮ አዲስ አበባ ላይ የሚደረገው ዓለማቀፍ የምልክት ቋንቋ አውደ ጥናት እንደ ሀገር ቋንቋውን በህግ ደረጃ የፀደቀ አንዱ ቋንቋ ለማድረግ የሚረዱ ጥናትና ምርምሮች ይገኙበታል ተብሎ ይታመናል ሲሉ ነግረውናል፡፡


15ተኛው ዓለማቀፍ የምልክት ቋንቋ አውደ ጥናት ከነገ ጥር 6 እስከ 9 2017ዓ.ም ድረስ ለ4 ተከታታ ቀናት አዲስ አበባ ውስጥ ይካሄዳል፡፡



በረከት አካሉ

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page