top of page

ጥር  30፣2016 - አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬተር ሆነው ተሾሙ

  • sheger1021fm
  • Feb 8, 2024
  • 1 min read

ዛሬ በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት አቶ ተመስገን ጥሩነህን ተክተው ሬድዋን ሁሴን የብሔራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡


የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ሆነው ሲሰሩ የቆዩትን የሬድዋን ሁሴንን አዲስ ሹመት መረጃ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ነው ያወጣው፡፡



በተጨማሪም አቶ ሰለሞን ሶካን በመተካት ትዕግስት ሃሚድ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሹመዋል፡፡ 

ትዕግስት ሃሚድ የተቋሙ ምክትል ዳይሬክተር ሆነው ሲሰሩ መቆየታቸው ተሰምቷል፡፡



የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…



Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page