ጠዋት፤ ማታ ኸረ እንደውም ቀንም ከስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ውጪ ሳይቀር የአዲስ አበባ #የትራንስፖርት_ችግር ተቃሎ አይታይም፡፡
ህዝቡ ታክሲ፣ አውቶብስ ጥበቃ ፀሐዩንም ዝናቡንም ችሎ በረዣዥም ሰልፎች ይታያል፡፡
የትራንስፖርት ያለህ እያለ ያማርራል፡፡
ከተማዋ አንድ ሰሞን ተገዙበት በተባለው ዋጋቸው የተነሳ መነጋገሪያ የሆኑት #አውቶብሶች ጨምሮ የትራንስፖርት ችግሩን ለመፍታት የተለያዩ ስራዎችን መስራቷ ትናገራለች፡፡
ግን መፍትሄው አይታይም፡፡ ዛሬም የትራንስፖርት ችግሩ ፀንቶ ይታያል፡፡ ችግሩ ለምን አልቃለል አለ?
ምህረት ስዩም
Comments