top of page

ጥር 29 2017 - በኢትዮጵያ ያለውን የቤት ችግር ለመፍታት የቤቶች የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ማቋቋም ያስፈልጋል ተባለ

  • sheger1021fm
  • Feb 6
  • 1 min read

በኢትዮጵያ ያለውን የቤት ችግር ለመፍታት የቤቶች የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ማቋቋም ያስፈልጋል ተባለ፡፡


ይህ የተባለው የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የቤት አቅርቦትና ፍላጎትን ለማጣጣም ባስጠናው ጥናት ነው፡፡

ጥናቱን ያጠናው የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ነው፡፡


በኢትዮጵያ ባሉ ከተሞች ያለውን የቤት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በአማካኝ በየአመቱ ከ471,000 በላይ ቤቶችን መገንባት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡


ጥናቱን ያቀረቡት በፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተመራማሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ጥላሁን በኢትዮጵያ ያለውን የቤት ችግር ለመፍታት የቤቶች ፋይናንስ ኮርፖሬሽንን ማቋቋም ያስፈልጋል ብለዋል፡፡


ኮርፖሬሽኑ ለቤት ገንቢዎች የፋይናንስ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡


ተጠሪነቱም ለብሔራዊ ባንክ እንዲሆን ተጠይቋል፡፡


በኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የቤት ችግር ለመፍታት መንግስት ከካፒታል በጀቱ 5 በመቶውን እንዲመድብም ተጠይቋል፡፡


አሁን ያለውን የቤት እጦት ችግር ለመፍታት የሪል ስቴት አልሚዎችን የሚያበረታቱ ፖሊሲዎችን መቅረፅ፣ የግሉ ዘርፍ በቤት ግንባታ ዘርፍ እንዲሳተፍ የሚያስችሉ ፖሊሲዎችን ማውጣት፣ የሞርጌጅ ባንኮችን ማቋቋም እንደሚያስፈልግል ተነግሯል፡፡


አሁን ላይ በኢትዮጵያ ከ70 በመቶ በላይ የሚሆኑ ቤቶች ከደረጃ በታች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page