top of page

ጥር  29፣2016 - የአፍሪካ ቡና ሳምንት አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ

  • sheger1021fm
  • Feb 7, 2024
  • 1 min read

የኢትዮጵያን ቡና በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስታወዋወቅና የገበያ እድል ለመፍጠር ይረዳል የተባለ ለ4 ቀን የሚቆይ የአፍሪካ ቡና ሳምንት አውደ ርዕይ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከፈተ፡፡

 

በአውደ ርዕይው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ በኢትዮጵያ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቡና ላይ ሕይወታቸውን መስርተዋል ብለዋል፡፡

 

በአለም አቀፍ ደረጃ የቡና ዋጋ እየቀነሰ ቢመጣም ኢትዮጵያ ግን በ2016 1.4 ቢሊየን ዶላር በ2015 ደግሞ 1.3 ቢሊየን ዶላር አግኝታለች ሲሉ አስረድተዋል፡፡

 

ለዚህም ምክንያት በቀደመዉ አሰራር ላይ ማሻሻያ መደረጉ፣ የቁጥጥር ስራው የበረታ መሆኑ እንዲሁም  ባለስልጣኑ ከፍተኛ ትኩረት ለቡና ጥራት መስጠቱ  ከሚበዙት ጥቂቶቹ ናቸዉ ተብሏል፡፡

 

መድረኩ የቡና ልማት ላይ ያሉ ተዋንያኖች ገፅ ለገፅ የሚመክሩበትና የሚወያዩበት እንደሚሆን ተሰምቷል፡፡

 

በአውደ ርዕዩ ላይ የተለያዩ አለም አገራት ቡና ላኪዎች ተቀባዮች እና አርሶ አደሮች ተገኝተዋል፡፡

 

ይህም ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ቡና እንድታስተዋውቅ እድል ይሰጣል ተብሏል፡፡

 

በ4 ቀን በሚቆየው አውደ ርዕይ ቡና ላይ ያሉ ችግሮች ምንድናቸው እና እንዴት ይፈታሉ የሚሉ ፁሁፎች ይቀርባሉ ተብሏል፡፡

 


ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አገራት ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ቡና ጠጪ ያለባት አገር ነች ተብሏል፡፡

 

በዚህም በአፍሪካ አህጉር ከሚጠጣው ቡና 50 በመቶ የሚሆነው በኢትዮጵያዊያን እንደሆነ ተነግሯል፡፡

 

የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን በተያዘው በጀት ዓመት 1.75 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ለማግኘት አስታውሷል፡፡

 

 

ያሬድ እንዳሻው

 

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

 




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page