top of page

ጥር 28 2017 - ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ለጊዜው አገልግሎት አይሰጥም ተባለ

ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የሀገር ውስጥ መንገደኞች ማስተናገጃ ሕንፃ ለጊዜው አገልግሎት አይሰጥም ተባለ።


ወደ በረራ ይዞ መግባት ከሚከለከሉ ቁሶችም መካከል ከመንገደኞች የሚሰበሰብ የሲጋራ መለኮሻ (ላይተር) ጊዜያዊ የማስቀመጫ ስፍራ ውስጥ ጭስ በመከሰቱ ነው አገልግሎቱ የተቋረጠው ተብሏል።

ለመንገደኞች ደህንነት ሲባል ሕንፃው ለጊዜው አገልግሎቱን እንዳቋረጠ አየር መንገዱ ተናግሯል።


በመሆኑም በዛሬው ዕለት ወደ ሀገር ውስጥ መዳረሻዎቻችን የምትጓዙ መንገደኞቻች በዓለም አቀፍ መንገደኞች ማስተናገጃ ተርሚናል በኩል ወደ በረራችሁ እንድትሳፈሩ አየር መንገዱ አሳስᎆል።


ከነገ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በተለመደው የሀገር ውስጥ ተርሚናል አገልግሎት መስጠት እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተናግሯል።


ለተፈጠረው መጉላላት አየር መንገዱ መንገደኞቹን ይቅርታ ጠይቋል።

Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page