top of page

ጥር 27፣2017 - የተለያዩ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች በማሳተፍ እየሰራሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ተናገረ

ኢትዮጵያ በግብርና፣ በጤናው፣ በትምህርት ያለባትን ችግር ለመቅረፍ የተለያዩ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች በማሳተፍ እየሰራሁ ነው ሲል የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ ተናገረ፡፡


ዲያስፖራው በኢትዮጵያ የሚገኙ ስራ ፈጣሪ ወጣቶች የገንዘብ ችግር ሳይገጥማቸው የማህበረሰቡን ችግር መቅረፍ የሚችሉ ስራዎችን እንዲሰሩ አግዛለሁኝ ብሏል፡፡


ዘመኑ የደረሰበት ቴክኖሎጂ መጠቀም ደግሞ ሌላው የሚበረታታ ተግባር ነው ሲልም ተናግሯል፡፡


እነዚህ ወጣቶች ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተሰባሰቡ እንደሆኑም ሰምተናል፡፡


የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ትረስት ፈንድ በትምህርት በጤናና በግብርና የሀገሪቱን ችግር ያቃልላሉ ተብለው የተከወኑ ስራዎችን አወዳድሮ የሽልማት መረሃግብርም አከናውኗል፡፡


ከዚህ ቀደም በሌላ ሌላም ስራ ተሰማርቶ እንደነበርና አሁን ጊዜ የሚፈልገው ይሄን በመሆኑ ፊቱን ወደዚ እንዳዞረ ነግሮናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….




ማርታ በቀለ



コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page