top of page

ጥር 27፣2017 - በሀይማኖት ተቋማት የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች በህጉ እንዴት ይታያል

በተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት ውስጥ የሚያገለግሉ ሰዎች ገንዘብ ወሰዱ፣ ሙስና ፈፀሙ ሲባል ይሰማል፡፡


በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ የሚፈፀምን #ሙስና ወይም ሌብነት መቆጣጠሪያ መላ ወይም ህግ አለ ወይ?


የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በመንግስት እና ህዝባዊ ተቋማት ላይ የሚደረጉ የሙስና ወንጀሎችን ተከታትዬ ለፍትህ ተቋማት አቀርባለሁ ይላል፡፡


ይሁንና እነዚህ የሃይማኖት ተቋማት ላይ የሚደረጉ የሙስና ወንጀሎችን የምከታተል ስልጣን እንደሌለው ተናግሯል፡፡


ኮሚሽኑ ከማይመለከታቸው ተቋማት መካከል የሃይማኖት ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እንዲሁም እድርን የመሳሰሉትን የመመርመር እና የማጣራት ስልጣን የለውም ሲሉ የነገሩን በስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ ናቸው፡፡


በሀይማኖት ተቋማት የሚፈፀሙ የሙስና ወንጀሎች በህጉ እንዴት ይታያል ስንል የህግ ባለሞያ የሆኑትን አቶ ተጠምቀ ዮሀንስን ጠይቀናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….




ማርታ በቀለ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page