top of page

ጥር 25፣ 2015- የሩሲያ ጦር በምስራቃዊ ዩክሬይን ዳኔስክ ግዛት የምትገኘውን የባህሙት ከተማን በሙሉ ከበባ ውስጥ ማስገባቱ ተሰማ


የሩሲያ ጦር በምስራቃዊ ዩክሬይን ዳኔስክ ግዛት የምትገኘውን የባህሙት ከተማን በሙሉ ከበባ ውስጥ ማስገባቱ ተሰማ፡፡


የሩሲያ ሀይሎች ወደ ከተማዋ የሚያመራውን ዋነኛ አውራ ጎዳና ተቆጣጥረውታል መባሉን CGTN ፅፏል፡፡


የዩክሬይኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ምዕራባዊያን እና ሌሎች አጋሮቻቸው ዘመን አፈራሽ የጦር አውሮፕላኖችን እንዲያቀርቡላቸው እየጎተጎቱ ነው፡፡


ቀደም ሲል ከተደጋጋሚ ጥያቄ በኋላ አሜሪካ አብራምስ፤ ጀርመን ደግሞ ሊዮፓርድ ታንኮችን ለዩክሬይን ለመስጠት ቃል ገብተውላታል፡፡


ዩክሬይን F-16 የጦር አውሮፕላኖች እንዲሰጧት ብትጠይቅም የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን ይሄን ማድረግ አንችልም ያሉት ሰሞኑን ነው፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Commentaires


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page