top of page

ጥር 23 2017 - ''የሀብት ምንጭ ማረጋገጥ ምዝገባ በፍትህ ተቋማት ክትትል ከማድረግ ጋር ተያይዞ ውስንነት ታይቶበታል''

በበጀት ዓመቱ 6 ወራት የሀብት ምንጭ ማረጋገጥ ምዝገባ በፍትህ ተቋማት ክትትል ከማድረግ ጋር ተያይዞ ውስንነት ታይቶበታል ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናገሩ፡፡


ይህ የተባለው የፌዴራል የስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የስድስት ወር የስራ አፈፃፀሙን ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡


በዚህም ውስንነት እና የአፈፃፀም ድክመት ታይቶባቸዋል የተባሉ ጉዳዮች በዝርዝር ቀርቧል፡፡


ተገኝቶባቸዋል ከተባሉት መካከል የአቅም ግንባታ ስራ፡ የበየነ መረብ ስልጠና፡ የከፍተኛ አመራሮች እና የሰራተኞች አቅም ግንባታ ስልጠና፡፡


በፀረ ሙስና ጉዳዮች ትምህርታዊ ውይይቶችን በሚዲያ ከማቅረብ አኳያ፡ ጉድለቶች እንደታዩባቸው ተነስቷል፡፡


ሌላው የሙስና መከላከል ጥናት ስራዎች አፈፃፀማቸው ዝቅተኛና ያልተፈጸሙ እንዳሉም ተነግረዋል።


ከዚህ ቀደም ተጠናክሮ የማይሰጡ የነበሩ አሁን ግን በቋሚነት ከምንሰራው ስራዎች መካከል አንዱ የአቅም ግንባታ ስልጠና ነው ሲሉ የመለሱት የፌዴራልየስነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ ናቸው፡፡


የሀብት ማጣራቱ የተጓተተው ተደጋጋሚ የሆነ ማጣራት ስለምናደርግ ነው ሲሉ ተናግረዋል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..



ማርታ በቀለ





Comentarios


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page