top of page

ጥር 22 2017 - አቶ ብርሃኑ አዴሎ  የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው  ተሾሙ

  • sheger1021fm
  • Jan 30
  • 1 min read

አቶ ብርሃኑ አዴሎ  የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው  ተሾሙ፡፡


አቶ ብርሃኑ አዴሎ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው በምክር ቤቱ ተሹመዋል።


ቃል መሃላም ፈጽመዋል፡፡


አቶ ብርሃኑ የኢሰመኮ  ኮሚሽነር የሆኑት ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር  የስራ ዘመናቸው ያበቃውን  ዶ/ር ዳንኤል በቀለን በመተካት ነው።

ከዶ/ር ዳንኤል የሃላፊነት ጊዜ ማብቃት ብኋል ላለፉት አምስት ወራት ኢሰመኮን በተጠባባቂነት የመሩት  ራኬብ መሰለ ናቸው።


የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው የተሸሙት አቶ ብርሃኑ አዴሎ   


የቀድሞው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል  ነበሩ፡፡


የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተርነት  ሆነው መስራታቸውንም የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page