ጥር 20፣ 2015- የማላዊው ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ በአገሪቱ በመዛመት ላይ የሚገኘው የኮሌራ ወረርሽኝ የአየር ለውጡ ውጤት እንደሆነ አምናለሁ አሉ
- sheger1021fm
- Jan 28, 2023
- 1 min read

የማላዊው ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ በአገሪቱ በመዛመት ላይ የሚገኘው የኮሌራ ወረርሽኝ የአየር ለውጡ ውጤት እንደሆነ አምናለሁ አሉ፡፡
የጉዳዩ ተያያዥነት ሊጠና ይገባል ማለታቸውን ቻናል አፍሪካ በድረ ገፁ ፅፏል፡፡
በማላዊ የኮሌራ ወረርሽኝ ከተቀሰቀሰ 10 ወራት ሆኖታል፡፡
እስካሁንም ወረርሽኙ ከሺህ በላይ ሰዎች መጨረሱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡
የአሁኑ የኮሌራ ወረርሽኝ በ20 ዓመታት ጊዜ እጅግ ከባዱ ነው ተብሏል፡፡
ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ የአሁኑን የኮሌራ ወረርሽኝ ከአየር ለውጡ ክስተት ጋር አያይዘው ማንሳታቸው ተሰምቷል፡፡
የኔነህ ከበደ
ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Comments