top of page

ጥር 20፣ 2015- የማላዊው ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ በአገሪቱ በመዛመት ላይ የሚገኘው የኮሌራ ወረርሽኝ የአየር ለውጡ ውጤት እንደሆነ አምናለሁ አሉ

  • sheger1021fm
  • Jan 28, 2023
  • 1 min read

የማላዊው ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ በአገሪቱ በመዛመት ላይ የሚገኘው የኮሌራ ወረርሽኝ የአየር ለውጡ ውጤት እንደሆነ አምናለሁ አሉ፡፡


የጉዳዩ ተያያዥነት ሊጠና ይገባል ማለታቸውን ቻናል አፍሪካ በድረ ገፁ ፅፏል፡፡


በማላዊ የኮሌራ ወረርሽኝ ከተቀሰቀሰ 10 ወራት ሆኖታል፡፡


እስካሁንም ወረርሽኙ ከሺህ በላይ ሰዎች መጨረሱ በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የአሁኑ የኮሌራ ወረርሽኝ በ20 ዓመታት ጊዜ እጅግ ከባዱ ነው ተብሏል፡፡


ፕሬዘዳንት ላዛረስ ቻክዌራ የአሁኑን የኮሌራ ወረርሽኝ ከአየር ለውጡ ክስተት ጋር አያይዘው ማንሳታቸው ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page