top of page

ጥር 20፣ 2015- በኢራን አንድ ታጣቂ በአዘርባጃን ኤምባሲ ላይ በከፈተው ጥቃት የጥበቃ ሀላፊውን መግደሉ ተሰማ


በኢራን አንድ ታጣቂ በአዘርባጃን ኤምባሲ ላይ በከፈተው ጥቃት የጥበቃ ሀላፊውን መግደሉ ተሰማ፡፡


በጥቃቱ ሁለት የጥበቃ ባልደረቦች ደግሞ አካላዊ ጉዳት እንደገጠማቸው ዘ ቴሌግራፍ ፅፏል፡፡


ጥቃት አድራሹ ወዲያውኑ መያዙ ታውቋል፡፡


አዘርባጃን እና በርካታ አገሮች ጥቃቱ የሽብር ጥቃት ነው በሚል ማውገዛቸው ተሰምቷል፡፡


የኢራን ሹሞች ግን ጥቃቱ የተፈፀመው በቤተሰብ ችግር ምክንያት ነው ብለዋል፡፡


ጥቃቱን በብርቱ ካወገዙ እና ከኮነኑት መካከል እስራኤል እና ሳውዲ አረቢያ እንደሚገኙበት በዘገባው ተጠቅሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page