top of page

ጥር 19 2017 - የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባኤን በማስመልከት የፓርቲው ም/ል ፕሬዘዳንት አደም ፋራህ መግለጫ ሰጥተዋል

  • sheger1021fm
  • Jan 27, 2025
  • 1 min read

ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ የሚካሄደውን #የብልፅግና_ፓርቲ ሁለተኛ ጉባኤን በማስመልከት የፓርቲው ምክትል ፕሬዘዳንት አደም ፋራህ ዛሬ ለጋዜጠኞች ጠቅለል ያለ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡


በአባላት ብዛት ፓርቲያቸው በአለም ላይ ከአንድ እስከ አስረኛ ደረጃ ከያዙ ፓርቲዎች አንዱ መሆኑንና በአሁኑ ወቅት ከ15.7 ሚሊዮን አባላት በላይ መያዙን ፓርቲው ምክትል ፕሬዘዳንት ተናግረዋል፡፡

ከ1,700 በላይ አባላቱ በፓርቲው ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ የተባለ ሲሆን ከ15 የማያንሱ የውጪ ሀገር ፓርቲዎችም በጉባኤ ላይ ለመገኘት እሽታቸውን መስጠታቸውንም አደም ፋራህ ተናግረዋል፡፡


“ከቃል እስከ ባህል” በሚል መሪ ቃል የፓርቲው ሁለተኛ ጉባኤ በአዲስ አበባው አደዋ አዳራሽ ለሁለት ቀናት ይደረጋል ያሉት የፓርቲው ምክትል ፕሬዘዳንት ከጉባኤ የተለያዩ ውጤቶች ይጠበቃል ብለዋል፡፡


የብልፅግና ፓርቲን ሁለተኛ ጉባኤን መሰረተት በማድረግ በተሰጠው መግለጫ ላይ፤ ጋዜጠኞች ጥያቄ መጠየቅ እንደማይችሉ በመነገሩ ከጉባኤው እና ከአጠቃላይ ከፓርቲው ጋር የተያያዙ ነጥቦችን በዚህ ወሬአችን ማካተት አልቻልንም፡፡


የኔነህ ሲሳይ

Recent Posts

See All
የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡

ጥር 12/2018 የኢትዮጵያ ሂሳብ አዋቂዎች እና ኦዲተሮች ማህበር "ስራቸውን በአግባቡ አልሰሩም፣ ህግን አላከበሩም ፣ ኦዲት ሪፖርት ለዓመታት አላቀረቡም ፣ጠቅላላ ጉባዔም ወቅቱን ጠብቀው ማካሄድ አልቻሉም"በሚል ከፍተኛ ቅሬታ የቀረበባቸውን የቦርድ አባላት በአዲስ ተካ፡፡ የቀድሞ ቦርድ አባላት ስራቸወን በአግባቡ ባለመ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page