top of page

ጥር 19፣2017 - ከነገ ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ በሁለቱም አቅጣጫች መንገዶች ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ እንደሚሆኑ ተነገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Jan 27
  • 1 min read

ከነገ ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ በሁለቱም አቅጣጫች መንገዶች ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ እንደሚሆኑ ተነገረ፡፡


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከነገ ጥር 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጣጫ መንገዶቹ ላልተወሰኑ ቀናት ዝግ እንደሚሆን ተናግሯል፡፡


በአዲስ አበባ በ2ኛው ዙር ከሚለሙት የኮሪደር መስመሮች መካከል የሰሚት- ጎሮ መንገድ አንደኛው መሆኑ አስታውሶ ከዚሁ ጋር በተያያዘ በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የሲ ኤም ሲ- ፔፕሲ - ጎሮ - መንገድ ልዩ ቦታው ሳፋሪ መብራት አካባቢ ብሪቲሽ ትምህርት ቤት አጠገብ የመንገድ ቆረጣ ይከወናል ተብሏል።


በዚህም መሰረት ከነገ ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከፊጋ - ወደ ሳፋሪ እንዲሁም ከሳፋሪ -ወደ ፊጋ የሁለቱም አቅጣጫ መንገዶቹ ዝግ እንደሚሆኑ ባለስልጣን መ/ቤቱ ተናግሯል።


የመንገዱ ተጠቃሚ አሽከርከሪዎች ይህንን አውቀው አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ሲል የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አሳስቧል፡፡

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page