top of page
  • sheger1021fm

ጥር 19፣ 2015- 2014 የትምህርት ዘመን 12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል 1,161 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉ


2014 የትምህርት ዘመን 12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል 1,161 ትምህርት ቤቶች አንድም ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም ተባለ፡፡


በሌላ በኩል 7 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ አምጥተዋል ሲሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል፡፡


ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ ያሳለፉት ትምህርት ቤቶች ደሴ ልዩ አዳሪ ት/ቤት፣ ኦዳ ልዩ አዳሪ ት/ቤት፣ ባህርዳር ስቴም ት/ቤት፣ ወላይታ ሊቃ ት/ቤት፣ የጎንደር ማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት እና ከግል ለባዊ ት/ቤት መሆናቸውን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡


የ12 ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች ከ50 በመቶ በላይ ያመጡት 3.3 በመቶ ብቻ መሆናቸው ተናግሯል፡፡


ፈተናውን በትክክል ከወሰዱት 896,520 ተማሪዎች ውስጥ ከግማሽ ወይንም ከ50 በመቶ በላይ ያመጡት፤ 29,909 መሆናቸውን ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስረድተዋል።


በዚህም መሰረት ከግማሽ በላይ ያመጡት 29,909 ተማሪዎች በቀጥታ ወደ ዩኒቨርስቲ ገብተው የአንደኛ ዓመት ተማሪ ይሆናሉ።


ወደ ዩኒቨርስቲ የሚያስገባቸወን ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን በተመለከት የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አሰራር ለመከተል ማቀዱን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።


ተመስገን አባተ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz




Recent Posts

See All

በኢትዮጵያ የካፒታል ወይም ድርሻዎች ገበያ መሳተፍ ለሚፈልጉ ተቋማት ከ3 እስከ 6 ወር ባለው ጊዜ ፍቃድ መስጠት ይጀመራል ተባለ። ፍቃድ የሚሰጣቸውን ተቋማት ለመለየት መመሪያ መዘጋጀቱን የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብሩክ ታዬ ተናግረዋል። የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ የተመለከተ ምክክር

በጋሞ ዞን ውስጥ የሚገኙ የዘይሴ እና የቁጫ ብሔረሰቦች ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ነው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑ እንደራሴዎች ተናገሩ፡፡ ለሚደርሰው በደል ዋነኛው ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በምርጫ ወቅት የተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲን በመምረጣቸው ነው ብለዋል፡፡ ንጋቱ ሙሉ ሸገርን ወሬዎች፣ መ

በአፋርና በአማራ ክልል በጦርነቱ ምክንያት የወደሙ ት/ቤት መልሶ መገንቢያ እስካሁን 2.8 ቢሊየን ብር ተሰብስቧል ተባለ፡፡ በጦርነቱ ከ300 ት/ቤቶች በላይ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ይታወሳል፡፡ ተመስገን አባተ ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

bottom of page