ጥር 17፣2016 - አቶ ደመቀ መኮንን ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ለቀቁ
- sheger1021fm
- Jan 26, 2024
- 1 min read
አቶ ደመቀ መኮንን ከብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትነት ለቀቁ፡፡
የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ የፓርቲውን የአመራር የመተካካት መርህንና የአሰራር ስርዓት በመከተል ዛሬ ባካሄደው ማጠቃለያ ስብሰባ አቶ ደመቀ መኮንንን በሙሉ ድምፅ በክብር ሸኝቷል ተብሏል፡፡
በአቶ ደመቀ ምትክም የፓርቲው ስራ አስፈጻሚ አባል የነበሩት አቶ ተመስገን ጥሩነህን ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው በአብላጫ ድምጽ መመረጣቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
ብልጽግና ፓርቲ ሁለት ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሲኖሩት አንደኛው አቶ አደም ፋራህ ናቸው፡፡
ሌላኛው ዛሬ በአቶ ተመስገን ጥሩነህ የተተኩት አቶ ደመቀ መኮንን ነበሩ፡፡

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comments