top of page

ጥር 17፣ 2015- የካሜሩን መንግስት ማንኛውም የውጭ ሀይል እንዲሸመግለን አንሻም አለ

  • sheger1021fm
  • Jan 25, 2023
  • 1 min read

የካሜሩን መንግስት ማንኛውም የውጭ ሀይል እንዲሸመግለን አንሻም አለ፡፡


በቅርቡ ካናዳ የካሜሩን ተፋላሚዎችን ለማደራደር ተሰናድቻለሁ ፤ ለዚህም የተደራዳሪዎቹን ይሁንታ አግኝቻለሁ የሚል መግለጫ አውጥታ እንደነበር ዘ ግሎብ ሜይል አስታውሷል፡፡


የካሜሩን መንግስት የውጭ ሀይሎችን ሽምግልና እና አደራዳሪነት አንሻም ማለቱ ካናዳን ኩም አድርጓታል፡፡


የካሜሩን መንግስት ጦር በአገሪቱ ሰሜን እና ደቡብ ምዕራብ ግዛቶች ከሚገኙ የመገንጠል አቀንቃኞች ጋር ሲዋጋ 7 አመታትን አስቆጥሯል፡፡


የውጭ ሀይሎችን አደራዳሪነት በጭራሽ አንቀበልም ያለው የካሜሩን መንግስት ጉዳዩ የውስጥ ችግራችን ስለሆነ ለእኛው ተውልን ማለቱ ተሰምቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page