top of page

ጥር 17፣ 2015- በአሜሪካ የቀድሞ ምክትል ፕሬዘዳንት ማይክ ፔንስ የኢንዲያና መኖሪያ ቤት ውስን የመንግስታዊ ሚስጥር ሰነዶች ተገኙ ተባለ

  • Jan 25, 2023
  • 1 min read

በአሜሪካ የቀድሞ ምክትል ፕሬዘዳንት ማይክ ፔንስ የኢንዲያና መኖሪያ ቤት ውስን የመንግስታዊ ሚስጥር ሰነዶች ተገኙ ተባለ፡፡


የአሜሪካ ፌዴራል የምርመራ ቢሮ (FBI) ባለሙያዎች ቀደም ሲል በፔንስ የኢንዲያና መኖሪያ ቤት ባካሄዱት ብርበራ ጥብቅ መንግስታዊ የሚስጥር ሰነዶቹ ላይ እንደረሱባቸው ዘጋርዲያን ፅፏል፡፡


በቅርቡ በአሜሪካው ፕሬዘዳንት ጆ ባይደን የዋሽንግተን የግል ቢሮ እና በዴላዌር መኖሪያ ቤታቸው በምክትል ፕሬዘዳንትነታቸው ዘመን እጃቸው የገቡ የመንግስታዊ ሚስጥራት ሰነዶች መገኘታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡


እነዚህ ሰነዶች የምክትል ፕሬዘዳንትነት የሀላፊነት ዘመናቸው እንዳበቃ ለአገሪቱ ብሔራዊ መዝገብ ቤት መተላለፍ የነበረባቸው ናቸው ይባላል፡፡


ከፔንስ መኖሪያ ቤት በተገኙት ሰነዶች ጉዳይ ምርመራ መጀመሩ ታውቋል፡፡


ጆ ባይደን በቀድሞው ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ የአስተዳደር ዘመን፣ ማይክ ፔንስ ደግሞ የዶናልድ ትራምፕ ምክትል እንደነበሩ ለትውስታ ተነስቷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Recent Posts

See All
የነሐሴ 9 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ኮንጎ የኮንጎ ኪንሻሣው የኢቦላ ወረርሽኝ አድማሱን እያሰፋ ነው ተባለ፡፡ ወረርሽኙ ወደ ተጨማሪ ግዛትም መዛመቱን የአፍሪካ የበሽታዎች መከላከያ እና መቆጣጠሪያ /አፍሪካ CDC/ መረጃ ማሳየቱን አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡ በኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ ያዳረሳቸው ግዛቶች ብዛት 6 ደርሷል፡፡ ኢቱሪ ወረርሽኙ ከፍተኛ ጫና ያሳደረ

 
 
 
የነሐሴ 8 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#የተባበሩት_አረብ_ኢሚሬትስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በሆርሙዝ ወሽመጥ በሁለት መርከቦቼ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ያለቻትን ኢራንን በብርቱ ኮነነቻት ተባለ፡፡ ኢራን በነዳጅ ጫኝ መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ሲል ከበድ ያለ ተቃውሞውን ያሰማው የኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሆነ አልጀዚራ እና AFP ፅፈዋ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page