top of page

ጥር 16 2017 - ‘’ከመስከረም አጋማሽ እስከ ታህሳስ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ብቻ 213 ሰዎች ከፍርድ ውጪ ተገድለዋል’’ ኢሰመኮ

  • sheger1021fm
  • Jan 24
  • 1 min read

በአማራ ክልል በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ 129 ንጹሃን ሰዎች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ተናገረ፡፡


በኦሮሚያ ክልል ደግሞ 84 ሰዎች መገደላቸው ኮሚሽኑ ጠቅሷል፡፡


ከመስከረም አጋማሽ 2017 ዓ.ም እስከ ታህሳስ ወር 2017 ዓ.ም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ብቻ 213 ሰዎች ከፍርድ ውጪ መገደላቸውን ኮሚሽኑ አስረድቷል፡፡

ግድያዎቹን የፈፀሟቸውም የመንግስት የፀጥታ ሀይች፣ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሰው ታጣቂ ቡድን በተለምዶ (ፋኖ) እና በኦሮሚያ ክልል የሚቀሳቀሰው በተለምዶ (ሸኔ) መሆናቸውን ኮሚሽኑ በሪፖቱ አስፍሯል፡፡


ለንጹሃኑ ግድያ ምክንያት የሆነው በታጣቂዎቹ በኩል መንግስትን ትደግፋላችሁ፣ በመግስት የፀጥታ ሀይች በኩል ደግሞ ታጣቂዎቹን ትደግፋላችሁ በሚል እንደሆነ ኮሚሽኑ የዓይን እማኞችን እና የተጎጂ ቤተሰቦች በማነጋገር ያወጣው ሪፖርት ያስረዳል፡፡


ኮሚሽኑ በሪፖርቱ የዘፈቀደ ፣ ጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትህ እጦት ያጋጠማቸውን ፣ አስድዶ መወሰር ፣ እገታ እና ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ ታስረው የቆዩ ሰዎችን ፣ የተፈናቀሉ ሰዎችን እንዲሁም የንብረት መውደምን አካቷል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page