top of page

ጥር 15 2017 - ‘’ባንኮች ለኢንዱስትሪው ፋይናንስ ከማቅረብ ይልቅ የአጭር ጊዜ ትርፍ በሚያስገኙ በዘርፎች እንዳይቀጥሉ አሰራሩን መፈተሸ ያስፈለጋል’’ ሚኒስትር መላኩ አለበል

  • sheger1021fm
  • Jan 23
  • 1 min read

ባንኮች ለአምራች ኢንዱስትሪው ፋይናንስ ከማቅረብ ይልቅ በተለመደው መንገድ የአጭር ጊዜ ትርፍ ወደ ሚያስገኝና ስጋታቸው ዝቅተኛ በሆኑ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው እንዳይቀጥሉ አሰራሩን መፈተሸ ያስፈለጋል ሲሉ የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ተናገሩ፡፡


የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል ይህን ያሉት የመ/ቤታቸውን የ6 ክንውን ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ነው፡፡


ባንኮች ስጋታቸው ዝቅተኛ እና የአጭር ጊዜ ትርፍ ወደሚያስገኙ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው እንዳይቀሩ ማድረግ የሚልበትን አሰራር ማየት ይገባናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡



ሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም ለአምራች ዘርፉ ሲቀርብ የነበረው ከ13 በመቶ ያልበለጠው የብድር አቅርቦት ድርሻ ወደ 24 በመቶ እንዲያድግ የፖሊሲ አቅጣጫ ቢሰጥም እስካሁን የደረሰው ግን 16 በመቶ ነው ብለዋል፡፡


ለአነስተኛና መካከለኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች የስራ ማስኬጃ ብድር ባንኮች ካላቸው ካፒታል ከአንድ በመቶ ያልበለጠው ወደ 10.3 ከፍ እንዲል መደረጉን ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡


ለአምራች ዘርፉ ለግብዓት አገልግሎት ባለፉት 6 ወራት 468 ሚሊዮን ዶላር በላይ ብድር ለማቅረብ ታቅዶ ከ369 ሚሊዮን ዶላር በላይ ቀርቧል ብሏል፡፡


እቅዱን ማሳካት ያልተቻለው ደግሞ የውጪ ምንዛሬ ለማግኘት ባንኮች የሚጠይቁት የማስያዥያ ብር ከወትሮ ከፍ በማለቱ ነው ሲሉ አቶ መላኩ አለበል አስረድተዋል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

Kommentare


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page