ዎርልድ ቪዥን በወላይታ ዞን 5 ወረዳዎች እያስገነባው ያለሁት የንጹህ የመጠጥ ውሃ ግንባታ ለማጠናቀቅ የትራንስፎርመር እጥረት እንቅፋት ሆኖብኛል አለ።
ወርልድ ቪዥን በዞኑ በ5 ወረዳዎች 22 የውሃ ጉድጓዶችን የቆፈረ ሲሆን ከሁለቱ ጉድጓዶች በስተቀር ሌሎቹ ተሰርተው ወደ ስራ ገብተዋል ተብሏል።
ሁለቱ ጉድጒዶች ስራቸው ቢጠናቀቅም ትራንስፎርመር ባለመገኘቱ ጉድጓዶቹ ወደ ስራ አለመግባታቸው ተነግሯል።

ወርልድ ቪዥን ‘’ጌሻሮ ፕሮጀክት’’ በሚል በ5ቱ ወረዳዎች ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦትና የብልሀርዝያ እና የአንጀት ትላትል የመከላከል ስራ እየሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር እንድርያስ ሸቤው ነግረውናል።
የንጽህ መጠጥ ውሃ ጉድጓዶቹ በኤሌክትሪክ እና በሶላር ሀይል አገልግሎት ያገኛሉ ተብሏል።
የጌሻሮ የውሃ ፕሮጀክት የአካባቢው ነዋሪዎች የውሃ መሸጥና የተለያዩ የስራ እድሎች ተፈጥሮላቸዋል መባሉን ሰምተናል።
ፕሮጀክቱ ላለፉት 5 ዓመታት ሲሰራ ነበር የተባለ ሲሆን አሁን ላይ እየተጠናቀቀ ነው ተብሏል፡፡
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: https://tinyurl.com/yc6tfzsw
Website: https://www.shegerfm.com/
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il
Comentários